ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝታቸውን ጀምረዋል፡፡

162

 

ባሕር ዳር፡ የካቲት 22/2011 ዓ.ም(አብመድ) የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ለሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ነው ዛሬ የካቲት 22/ 2011 ዓ.ም አዲስ አበባ የገቡት፡፡

Image may contain: one or more people, people standing and outdoor

ፕሬዚዳንቱ ቦሌ ዓለም ዓቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ሁለቱ መሪዎች በሁለትዮሽ የኢኮኖሚ ጉዳዮች እንደሚመክሩ ይጠበቃል።
ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ ቆይታቸው በአዲስ አበባ በሚካሄደው የኢትዮ-ኬንያ ንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ እንደሚሳተፉም ይጠበቃል።

Image may contain: 5 people, people smiling, people standing and outdoor

በፎረሙ የሚሳተፉ 100 የኬንያ መንግስት ባለስልጣናት፣ የኮርፖሬት እና የንግድ ማህበረሰብ ተወካይ ኬንያዉያንም ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል።

Image may contain: 2 people, people standing

የንግድ እና ኢንቨስትመንት ፎረሙ ዓላማ ደግሞ በኢትዮጵያ እና በኬንያ መካከል ያለውን የንግድ እና የኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር መሆኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ፎቶ፡- ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት