ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ጄ.ብሊንከን ጋር ተወያዩ።

45
ነጭመደበኛ
ነጭመደበኛ

ባሕር ዳር፡ መጋቢት 06/2015 ዓ.ም (አሚኮ) አሕመድ ዛሬ ረፋድ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ከዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ጄ.ብሊንከን ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸውም በተለያዩ የሀገር ውስጥ፣ ቀጣናዊ እና የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን፥ በኢትዮጵያ እና በዩናይትድ ስቴትስ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ተስማምተዋል።
ኢትዮጵያ በሰላም ስምምነቱ ላይ እያስመዘገበች ያለችው ስኬት ተቀባይነት አግኝቷል። በኢኮኖሚው፣ በልማት ጥረቶች፣ በተለይም በግብርና እና በቀጣናዊ መረጋጋት ላይ ያሉ ጉዳዮችም ትኩረት ተሰጥቶባቸዋል። መረጃው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ነው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!