ባሕር ዳር: ጥር 03/2015 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ መንግሥት የሰላም ስምምነቱ ዳር እንዲደርስ በሙሉ ቁርጠኝነት እየሠራ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ ገለጹ፡፡
ዶክተር ለገሰ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፤ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሠረት የመከላከያ ሠራዊት ከህወሓት ታጣቂዎች ከባድ የጦር መሣሪያዎችን መረከብ ጀምሯል ብለዋል፡፡
ይህም የሰላም ስምምነቱ መሬት መንካት መጀመሩን የሚያመለክት መሆኑን ነው የገለጹት፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የሰላም ስምምነቱ ዳር እንዲደርስ በሙሉ ቁርጠኝነት እየሠራ መሆኑንም ነው ዶክተር ለገሰ የገለጹት፡፡
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!