ባሕር ዳር፡ መጋቢት 06/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል የላቀ ዉጤት አምጥታችሁ የውጭ ሀገር የትምህርት እድል/Scholarship / እድል ለተሰጣቸው 273 ተማሪዎች የውጭ ሀገር ትምህርቱ የሚጀመረዉ ከመስከረም 2016 ዓ.ም ጀምሮ በመኾኑ ቀደም ሲል ወደተመደቡባቸው ዩኒቨርስቲዎች እንዲገቡ አሳስቧል፡፡
ለውጭ ሀገር ትምህርታቸው የሚያግዝ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ከተመደቡባቸው ዩኒቨርስቲዎች ጋር በመነጋገር የሚፈጸም ይኾናል፡፡
በዚህ ጉዳይ በተናጠል ወደ ትምህርት ሚኒስቴር የሚመጣ ተማሪ የማይስተናግድ መኾኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል። መረጃው የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ነው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!