ቤላሩስ የሚገኙ ኩባንያዎች በኢንዱስትሪ ፓርኮች የተለያዩ ቁሳቁሶችን ማምረት እንደሚፈልጉ ገለጹ።

76
ባሕር ዳር :መጋቢት 15/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ተቀማጭነታቸውን ቤላሩስ ያደረጉ የተለያዩ ቁሳቁሶችን የሚያመርቱ ኩባንያዎች በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ለማምረት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።
ኩባንያዎቹ ለማዕድን ማውጣት አገልግሎት የሚውሉ መኪኖችና የሞተር ክፍሎችን እንዲሁም የህክምና ቁሳቁሶችን በኢንዱስትሪ ፓርኮች ለማምረት ነው ፍላጎታቸውን የገለጹት።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ፣ የኩባንያዎቹን ተወካዮች በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ኮርፖሬሽኑ ለኢንቨስትመንታቸው ዕውን መሆን ያልተቋረጠ ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።
ኮርፖሬሽኑ የሚያቀርባቸውን ኢንቨስትመንት ተኮር አገልግሎቶች፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ገንብቶ የሚያስተዳድራቸውን ኢንዱስትሪ ፓርኮች እንዲሁም የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎችና ምቹ ሁኔታዎችን የተመለከቱ ዝርዝር መረጃዎች ለኩባንያዎቹ አቅርበዋል።
ኩባንያዎቹም ስለኢንቨስትመንታቸውና መስራት ስለሚያስቡት ሥራ ዝርዝር መረጃዎችን ማቅረባቸውን ከኮርፖሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!